በቅርቡ በሐገራችን ኢትዮጵያ በተከሰተው አሳዛኝ መፈናቀል ምክንያት፣ ወገኖቻችን የጌድዮን ሕዝቦች ለከፍተኛ ችግርና ቃይ ተጋልጠዋል። ተወልደው እትብታቸው በተቀበረበት ሐገር ውስጥ፣ ቤት ኖሮዋቸው እንደ ውሻ ጎዳና ላይ ተጥለው፣ አርሰውና ዘርተው እራሳቸውን ከመገቡበት ቀያቸው ተባርረው ለማኞች ሆነዋል። ሐገር ኖሮዋቸው ኢትዮጵያ እናታችን በሚሏት ሐገር ስደተኞች ሆነዋል። መብታቸው ተረግጦ፣ ህልውናቸው ተደፍሮ፣ ባእድንና መንገደኛን በባህሏ በምታስተናግደው ኢትዮጵያ ሐገራቸው ውስጥ ለጠላት እንኳን የማይደረግ ግፍ ተፈፅሞባቸዋል።
እነዚህን እህቶቻችንን፣ ወንድሞቻችንን፣ እናቶቻችንንና አባቶቻችንን ካሉበት ስቃይ ለማዳን፣ ወገን ለወገኑ መድረስ ባህላችንና ልምዳችን ነውና፣ እሁድ ማርች 31 ቀን 2019 ከቀኑ 2፡00 ፒ.ኤም ጀምሮ (Sunday 31 March 2019, starting at 2:00 pm) በቁልቢ ገብርኤል ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን አዳራሽ ውስጥ የእርዳታ ማሰባሰብያ ፕሮግራም አዘጋጅተናል።
በዚህ ዝግጅት ላይ ተገኝተው ለሐገራችን የጌድዮን ሕዝብ እርዳታዎን እንዲለግሱ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የኢትዮጵያ ማህበር በለንደን ኦንታሪዮ